ከሁለት ቀናት በኋላ በሚጀመረው የዘንድሮው የ2024/25 የውድድር ዘመን የስፔን ላሊጋ አዳዲስ ህጎች ተግባራዊ እንደሚደረጉ ተገልጿል። ከእነዚህም መካከል :- - በቀጣይ ዳኞችን ከቡድኑ አምበል ውጪ ሌሎች ተጨዋቾች ማነጋገር አይችሉም። - ተጨማሪ ጉዳቶች ሲኖሩ ተጨማሪ ተጨዋች መቀየር ይቻላል። - አምስት ተጨዋቾች በአንድ ጊዜ ማሟሟቅ ይችላሉ። - በላሊጋው ጨዋታዎች አዲሱ የጨዋታ ውጪ ቴክኖሎጂ ( SAOT ) ተግባራዊ ያደርጋል። የዘንድሮው የ 2024/25 የውድድር ዘመን የስፔን ላሊጋ የፊታችን ሐሙስ የሚጀምር ይሆናል።
.